ኢሳይያስ 51:4-10 NASV

4 “ወገኔ ሆይ፤ አድምጠኝ፤ሕዝቤ ሆይ፤ ስማኝ፤ሕግ ከእኔ ይወጣል፤ፍርዴም ለሕዝቦች ብርሃን ይሆናል።

5 ጽድቄ በፍጥነት እየቀረበ፣ማዳኔም እየደረሰ ነው፤ክንዴም ለመንግሥታት ፍትሕን ያመጣል፤ደሴቶች ወደ እኔ ይመለከታሉ፤ክንዴንም በተስፋ ይጠብቃሉ።

6 ዐይኖቻችሁን ወደ ሰማያት አንሡ፤ወደ ታች ወደ ምድርም ተመልከቱ፤ሰማያት እንደ ጢስ በነው ይጠፋሉ፤ምድር እንደ ልብስ ታረጃለች፤ነዋሪዎቿም እንደ አሸን ፈጥነው ይረግፋሉ፤ማዳኔ ግን ለዘላለም ይኖራል፤ጽድቄም መጨረሻ የለውም።

7 “እናንት ጽድቅን የምታውቁ፣ሕጌንም በልባችሁ ያኖራችሁ ሰዎች ስሙኝ፤ሰዎች ሲዘብቱባችሁ አትፍሩ፤ሲሰድቧችሁ አትደንግጡ።

8 ብል እንደ ልብስ ይበላቸዋል፤ትል እንደ በግ ጠጒር ይውጣቸዋል፤ጽድቄ ግን ለዘላለም፣ማዳኔም ከትውልድ እስከ ትውልድ ጸንታ ትኖራለች።”

9 የእግዚአብሔር ክንድ ሆይ፤ተነሥ፤ ተነሥ! ኀይልን ልበስ፤እንዳለፉት ዘመናት፣በጥንት ትውልዶችም እንደሆነው ሁሉ ተነሥ።ረዓብን የቈራረጥህ፣ታላቁን ዘንዶ የወጋህ አንተ አይደለህምን?

10 የዳኑት እንዲሻገሩ ባሕሩን፣የታላቁን ጥልቅ ውሆች ያደረቅህ፣በጥልቁም ውስጥ መንገድ ያበጀህ፣አንተ አይደለህምን?