1 ጽዮን ሆይ፤ ተነሺ፤ ተነሺ፤ኀይልን ልበሺ፤ቅድስቲቱ ከተማ፤ ኢየሩሳሌም ሆይ!የክብር ልብስሽን ልበሺ፤ያልተገረዘ የረከሰምከእንግዲህ ወደ አንቺ አይገባም።
2 ትቢያሽን አራግፊ፤ኢየሩሳሌም ሆይ፤ ተነሺ በዙፋንሽ ላይ ተቀመጪ፤ምርኮኛዪቱ የጽዮን ልጅ ሆይ፤የዐንገትሽን የእስራት ሰንሰለት አውልቀሽ ጣዪ።
3 እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ያለ ዋጋ ተሸጣችሁ ነበር፤ያለ ገንዘብ ትቤዣላችሁ።”
4 ልዑል እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“በመጀመሪያ ሕዝቤ ይኖር ዘንድ ወደ ግብፅ ወረደ፤በኋላም አሦር ያለ ምክንያት አስጨንቆ ገዛው።