ኢሳይያስ 30:10-16 NASV

10 ባለ ራእዮችን፣“ከእንግዲህ ራእይን አትዩ” ይላሉ፤ነቢያትንም እንዲህ ይላሉ፤“እውነተኛውን ትንቢት ከእንግዲህ አትንገሩን፤ደስ የሚያሰኘውን ንገሩን፤የሚያማልለውን ተንብዩልን።

11 ከዚህ መንገድ ፈቀቅ በሉ፤ከጐዳናውም ራቁ፤ከእስራኤል ቅዱስ ጋርፊት ለፊት አታጋጥሙን።”

12 ስለዚህ፣ የእስራኤል ቅዱስ እንዲህ ይላል፤“ይህን ቃል ስላቃለላችሁ፣ግፍን ስለታመናችሁ፣ማታለልን ስለ ተደገፋችሁ፣

13 ስለዚህ ይህ ኀጢአት፣ተሰነጣጥቆ ሊወድቅ እንደ ደረሰ፣ሳይታሰብ ድንገት እንደሚወድቅ ረጅም ቅጥር ይሆንባችኋል።

14 ከስብርባሪዎቹም መካከል፣ለፍም መጫሪያ፣ለውሃ መጥለቂያ ገል እስከማይገኝ ድረስ፣ምንም ሳይቀር ክፉኛ እንደሚንኰታኰት፣የሸክላ ዕቃ ይደቃል።”

15 የእስራኤል ቅዱስ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“በመመለስና በማረፍ ትድናላችሁ፤በጸጥታና በመታመን ትበረታላችሁ፤እናንተ ግን ይህን አላደረጋችሁም፤

16 ደግሞም ‘አይሆንም፣ በፈረስ እንሸሻለን’ አላችሁ፤ስለዚህ ትሸሻላችሁ።ደግሞም፣ ‘በፈጣን ፈረስ እናመልጣለን’ አላችሁ፤ስለዚህ አሳዳጆቻችሁም ፈጣን ይሆናሉ።