ኢሳይያስ 57:4-10 NASV

4 የምትሣለቁት በማን ላይ ነው?የምታሽሟጥጡት ማንን ነው?ምላሳችሁንስ አውጥታችሁ የምታሾፉት በማን ላይ ነው?እናንት የዐመፀኞች ልጆች፣የሐሰተኞች ዘር አይደላችሁምን?

5 በባሉጥ ዛፎች መካከል፣ቅጠሉ በተንዠረገገ ዛፍ ሥር በዝሙት የምትቃጠሉ፣በሸለቆዎች፣ በዐለት ስንጣቂዎችም ውስጥልጆቻችሁን የምትሠዉ አይደላችሁምን?

6 በሸለቆው በሚገኙት ለስላሳ ድንጋዮችውስጥ ያሉት ጣዖቶች የአንቺ ናቸው፤እነርሱም ዕጣ ፈንታዎችሽ ናቸው፤ርግጥ ነው፣ በእነርሱ ላይ የመጠጥ ቊርባን አፍስሰሻል፤የእህል ቍርባንም አቅርበሻል፤ታዲያ፣ ስለ እነዚህ ነገሮች ዝም እላለሁን?

7 ዐልጋሽን ከፍ ባለውና በረጅሙ ኰረብታ ላይ አነጠፍሽ፤በዚያም መሥዋዕትሽን ልታቀርቢ ወጣሽ።

8 ከመዝጊያሽና ከመቃንሽ ጀርባ፣የጣዖት ምስሎችሽን ሰቀልሽ፤እኔን ትተሽ መኝታሽን ገላለጥሽ፤በላይም ወጥተሽ በጣም ገለጥሽው፤መኝታቸውን ከወደድሽላቸው ጋር ስምምነት አደረግሽ፤ዕርቃናቸውንም አየሽ።

9 የወይራ ዘይት ይዘሽ፣ሽቶ በላዩ ጨምረሽ ወደ ሞሎክ ሄድሽ፤መልእክተኞችሽን ወደ ሩቅ አገር ላክሽ፤እስከ ራሱ እስከ ሲኦልም ዘለቅሽ።

10 በመንገድ ብዛት ደከምሽ፤ነገር ግን ‘ተስፋ የለውም’ አላልሽም፤የጒልበት መታደስ አገኘሽ፤ስለዚህም አልዛልሽም።