ኢሳይያስ 65:5-11 NASV

5 ‘ዘወር በል፤ አትቅረበኝ፤አትጠጋኝ፤ እኔ ከአንተ ይልቅ ቅዱስ ነኝ’ የሚሉ ናቸው።እንዲህ ያለው ሕዝብ በአፍንጫዬ ዘንድ እንደ ጢስ፣ቀኑን ሙሉ እንደሚነድድ እሳት ነው።

6 “እነሆ፤ እንዲህ የሚል ተጽፎ በፊቴ ተቀምጦአል፤ዝም አልልም፤ ነገር ግን እንደ ሥራው እሰጠዋለሁ፤የእጃቸውንም እከፍላቸዋለሁ፤

7 የእናንተን ኀጢአት የአባቶቻችሁንም ኀጢአት እበቀላለሁ”ይላል እግዚአብሔር።“በተራሮች ላይ የሚቃጠል መሥዋዕት ስላቀረቡ፣በኰረብቶች ላይ ስለ ሰደቡኝ፣በሰፈሩት ቊና ይሰፈርባቸዋል፤ስለ ቀደሙት ሥራዎቻቸውም የእጃቸውን ያገኛሉ።”

8 እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“በወይኑ ዘለላ ውስጥ ጭማቂው ገና እንዳለ ሁሉ፣ሰዎችም፣ ‘በውስጡ ጥሩ ነገር ስላለአትቊረጡት’ እንደሚሉ፣እኔም ስለ ባሮቼ ስል እንዲሁ አደርጋለሁ፤ሙሉ በሙሉ አላጠፋቸውም።

9 ከያዕቆብ ዘር የሆኑትን፣ከይሁዳም ተራሮቼን የሚወርሱትን አመጣለሁ።የተመረጠው ሕዝቤ ይወርሳቸዋል፤ባሪያዎቼም በዚያ ይኖራሉ።

10 አጥብቀው ለሚፈልጉኝ ሕዝቤ፣ሳሮን የበጎች መሰማሪያ፣የአኮር ሸለቆም የከብቶች ማረፊያ ይሆናል።

11 “ነገር ግን እግዚአብሔርን ለተዋችሁት ለእናንተ፣የተቀደሰ ተራራዬን ለረሳችሁት፣‘ዕጣ ፈንታ’ ለተባለ ጣዖት ቦታ ላዘጋጃችሁት፣‘ዕድል’ ለተባለም ጣዖት ድብልቅ የወይን ጠጅ በዋንጫ ለሞላችሁት፣