ኢሳይያስ 65:7-13 NASV

7 የእናንተን ኀጢአት የአባቶቻችሁንም ኀጢአት እበቀላለሁ”ይላል እግዚአብሔር።“በተራሮች ላይ የሚቃጠል መሥዋዕት ስላቀረቡ፣በኰረብቶች ላይ ስለ ሰደቡኝ፣በሰፈሩት ቊና ይሰፈርባቸዋል፤ስለ ቀደሙት ሥራዎቻቸውም የእጃቸውን ያገኛሉ።”

8 እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“በወይኑ ዘለላ ውስጥ ጭማቂው ገና እንዳለ ሁሉ፣ሰዎችም፣ ‘በውስጡ ጥሩ ነገር ስላለአትቊረጡት’ እንደሚሉ፣እኔም ስለ ባሮቼ ስል እንዲሁ አደርጋለሁ፤ሙሉ በሙሉ አላጠፋቸውም።

9 ከያዕቆብ ዘር የሆኑትን፣ከይሁዳም ተራሮቼን የሚወርሱትን አመጣለሁ።የተመረጠው ሕዝቤ ይወርሳቸዋል፤ባሪያዎቼም በዚያ ይኖራሉ።

10 አጥብቀው ለሚፈልጉኝ ሕዝቤ፣ሳሮን የበጎች መሰማሪያ፣የአኮር ሸለቆም የከብቶች ማረፊያ ይሆናል።

11 “ነገር ግን እግዚአብሔርን ለተዋችሁት ለእናንተ፣የተቀደሰ ተራራዬን ለረሳችሁት፣‘ዕጣ ፈንታ’ ለተባለ ጣዖት ቦታ ላዘጋጃችሁት፣‘ዕድል’ ለተባለም ጣዖት ድብልቅ የወይን ጠጅ በዋንጫ ለሞላችሁት፣

12 ተጣርቼ ስላልመለሳችሁ፣ተናግሬ ስላልሰማችሁ፣በፊቴ ክፉ ነገር ስላደረጋችሁ፣የሚያስከፋኝን ነገር ስለ መረጣችሁ፣ለሰይፍ እዳርጋችኋለሁ፤ሁላችሁም ለመታረድ ትጐነበሳላችሁ።”

13 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ባሮቼ ይበላሉ፤እናንተ ግን ትራባላችሁ፤ባሮቼ ይጠጣሉ፤እናንተ ግን ትጠማላችሁ፤ባሮቼ ደስ ይላቸዋል፤እናንተ ግን ታፍራላችሁ።