1 “የይሁዳ ኀጢአት በብረት ብርዕ፣በሾለ የአልማዝ ጫፍ፣ ተጽፎአል፤በልባቸው ጽላት፣በመሠዊያቸውም ቀንዶች ላይ ተቀርጾአል።
2 ልጆቻቸው እንኳ ሳይቀሩ፣በለመለሙ ዛፎች ሥር፣ከፍ ባሉ ኰረብቶችም ላይ ያሉትን፣መሠዊያቸውንና አሼራ የተባለችውን ጣዖት ምስል ያስባሉ።
3 በአገርህ ሁሉ ከተፈጸመው ኀጢአት የተነሣ፣በምድሪቱ ያለህ ተራራዬ፣ሀብትህንና ንብረትህን ሁሉ፣መስገጃ ኰረብቶችህንም ጭምር፣ለብዝበዛ አደርገዋለሁ።
4 በገዛ ጥፋትህ፣የሰጠሁህን ርስት ታጣለህ፤በማታውቀውም ምድር፣ለጠላቶችህ ባሪያ አደርግሃለሁ፤ለዘላለም የሚነደውን፣የቍጣዬን እሳት ጭረሃልና።”
5 እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“በሰው የሚታመን፣በሥጋ ለባሽ የሚመካ፣ልቡንም ከእግዚአብሔር የሚያርቅ የተረገመ ነው።
6 በምድረ በዳ እንዳለ ቍጥቋጦ ይሆናል፤መልካም ነገር ሲመጣ አያይም፤ሰው በሌለበት በጨው ምድር፣በምድረ በዳ በደረቅ ስፍራ ይቀመጣል።
7 “ነገር ግን በእግዚአብሔር የሚታመን፣መታመኛውም እግዚአብሔር የሆነ ሰው ቡሩክ ነው።