1 የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤
2 “ሂድና ጮኸህ ይህን ለኢየሩሳሌም ጆሮ አሰማ፤“እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤‘በወጣትነትሽ ጊዜ የነበረሽን ታማኝነት፣በሙሽርነትሽም ወራት እንዴት እንደ ወደድሽኝ፣በምድረ በዳ ዘር በማይዘራበት ምድር፣እንዴት እንደተከተልሽኝ አስታውሳለሁ።
3 እስራኤል ለእግዚአብሔር ቅዱስ ነበረች፤የመከሩም በኵር ነበረች፤የዋጧት ሁሉ በደለኞች ሆኑ፤መዓትም ደረሰባቸው’ ”ይላል እግዚአብሔር።
4 የያዕቆብ ቤት ሆይ፤ የእስራኤል ቤት ወገን ሁላችሁ፣ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ።