ኤርምያስ 2:26-32 NASV

26 “ሌባ በተያዘ ጊዜ እንደሚያፍር፣የእስራኤልም ቤት አፍሮአል፤እነርሱ፣ ንጉሦቻቸውና ሹሞቻቸው፣ካህናታቸውና ነቢያታቸው እንዲሁ ያፍራሉ።

27 ዛፉን፣ ‘አንተ አባቴ ነህ’ድንጋዩንም፣ ‘አንተ ወለድኸኝ’ አሉ፤ፊታቸውን ሳይሆን፣ጀርባቸውን ሰጥተውኛልና፤በመከራቸው ጊዜ ግን፣‘መጥተህ አድነን’ ይላሉ።

28 ታዲያ፣ ልታመልካቸው ያበጀሃቸው አማልክት ወዴት ናቸው?በመከራህ ጊዜ ሊያድኑህ የሚችሉ ከሆነ፣ይሁዳ ሆይ፤ እስቲ ይምጡና ያድኑህ፤የከተሞችህን ቍጥር ያህል፣የአማልክትህም ብዛት እንዲሁ ነውና።

29 “ለምን በእኔ ታማርራላችሁ?ያመፃችሁብኝ እናንተ ሁላችሁ ናችሁ፤”ይላል እግዚአብሔር።

30 “ልጆቻችሁን በከንቱ ቀጣኋቸው፤እነርሱም አልታረሙም።ሰይፋችሁ እንደ ተራበ አንበሳ፣ነቢያታችሁን በልቶአል።

31 “የዚህ ትውልድ ሰዎች ሆይ፤ የእግዚአብሔርን ቃል አስተውሉ፤“እኔ ለእስራኤል ሕዝብ ምድረ በዳ፣ወይስ ድቅድቅ ጨለማ ያለበት ምድር ሆንሁበትን?ሕዝቤ፣ እንደ ልባችን ልንሆን እንፈልጋለን፤ተመልሰንም ወደ አንተ አንመጣም’ ለምን ይላል?

32 ለመሆኑ ቆንጆ ጌጣጌጧን፣ሙሽራ የሰርግ ልብሷን ትረሳለችን?ሕዝቤ ግን፣እጅግ ብዙ ቀን ረስቶኛል።