ኤርምያስ 22:11-17 NASV

11 በአባቱ ምትክ በይሁዳ ላይ ስለ ነገሠው፣ ከዚህ ስፍራ በምርኮ ስለ ተወሰደው፣ ስለ ኢዮስያስ ልጅ ስለ ሰሎ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፤ “ከእንግዲህ አይመለስም፤

12 ተማርኮ በሄደበት አገር ይሞታል እንጂ ይህቺን ምድር ዳግመኛ አያይም።”

13 “ቤተ መንግሥቱን በግፍ ለሚሠራ፣ሰገነቱንም ፍትሕ በማዛባት ለሚገነባ፣ወገኑን በነጻ ለሚያሠራ፣የድካሙንም ዋጋ ለማይከፍለው፣

14 ‘ባለ ትልልቅ ሰገነት፣ሰፊ ቤተ መንግሥት ለራሴ እሠራለሁ’ ለሚል ወዮለት!ሰፋፊ መስኮቶችን ያበጅለታል፤በዝግባ እንጨት ያስጌጠዋል፤ቀይ ቀለምም ይቀባዋል።

15 “በዝግባ ዕንጨት ብዛት፣የነገሥህ ይመስልሃልን?አባትህስ ፍትሕንና ጽድቅን በማድረጉ፣የሚበላውና የሚጠጣው ጐድሎት ነበርን?እነሆ፣ ሁሉም መልካም ሆነለት።

16 የድኾችንና የችግረኞችን ፍትሕ አላጓደለም፤ስለዚህም ሁሉ መልካም ሆነለት።እኔን ማወቅ ማለት ይህ አይደለምን?”ይላል እግዚአብሔር።

17 “የአንተ ዐይንና ልብ ያረፉት ግን፣አጭበርብሮ ጥቅምን በማግኘት፣የንጹሑን ደም በማፍሰስ፣ጭቈናንና ግፍን በመሥራት ላይ ብቻ ነው።