ኤርምያስ 3:2-8 NASV

2 “እስቲ ቀና ብለሽ ጭር ያሉትን ኰረብቶች ተመልከቺ፣በርኵሰት ያልተጋደምሽበት ቦታ ይገኛልን?በበረሓ፣ እንደ ተቀመጠ ዘላን ዐረብ፣በየመንገዱ ዳር ተቀምጠሽ ወዳጆችሽን ጠበቅሽ።በዝሙትሽና በክፋትሽ፣ምድሪቱን አረከስሽ።

3 ስለዚህ ካፊያ ተከለከለ፤ኋለኛው ዝናብም ጠፋ።አንቺ ግን አሁንም የጋለሞታ ገጽታ አለብሽ፤ዐይንሽን በዕፍረት አልሰብር ብለሻል።

4 አሁንም ወደ እኔ ተጣርተሽ፣‘አባቴ፣ የልጅነት ወዳጄ፣

5 ሁል ጊዜ ትቈጣለህን?ቍጣህስ ለዘላለም ነውን?’ አላልሽኝም?የምትናገሪው እንዲህ ነው፤ይሁን እንጂ የቻልሽውን ክፋት ሁሉ ታደርጊያለሽ።”

6 እግዚአብሔር በንጉሥ ኢዮስያስ ዘመን እንዲህ አለኝ፤ “ከዳተኛዪቱ እስራኤል ያደረገችውን አየህን? ከፍ ወዳለው ኰረብታ ሁሉ ወጥታ፣ ወደ ለመለመው ዛፍ ሥር ሁሉ ሄዳ በዚያ አመነዘረች።

7 ይህን ሁሉ ካደረገች በኋላ፣ ወደ እኔ ትመለሳለች ብዬ ነበር፤ ሆኖም አልተመለሰችም፤ ከሓዲዋ እኅቷ ይሁዳም ይህን አየች።

8 ለከዳተኛ ዪቱ እስራኤል ስለ ምንዝርናዋ ሁሉ የፍች ወረቀቷን ሰጥቼ አባረርኋት። ከሓዲዋ እኅቷ ይሁዳም ይህን አይታ እንዳልፈራች አየሁ፤ ወጥታም አመነዘረች።