1 እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“እነሆ፤ በባቢሎንና በምድሯ ላይ፣የሚያጠፋ ነፋስ አስነሣለሁ።
2 እንዲያበጥሯትና እንዲያወድሟት፣ባዕዳንን በባቢሎን ላይ እልካለሁ፤በመከራዋም ቀን፣ከበው ያስጨንቋታል።
3 ቀስተኛው ቀስቱን እስኪገትር፣የጦር ልብሱንም እስኪለብስ ፋታ አትስጡት፤ለወጣቶቿ አትዘኑ፤ሰራዊቷንም ፈጽማችሁ አጥፉ።
4 በባቢሎን ምድር ታርደው፣በአደባባዮቿም እስከ ሞት ቈስለው ይወድቃሉ።
5 ምድራቸው በእስራኤል ቅዱስ ፊት፣በበደል የተሞላች ብትሆንም፣እስራኤልንና ይሁዳን አምላካቸው፣የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር አልጣላቸውም።