ኤርምያስ 51:21-27 NASV

21 በአንቺ ፈረሱንና ፈረሰኛውን እሰባብራለሁ፤በአንቺ ሠረገላውንና ሠረገላ ነጂውን እሰባብራለሁ፤

22 በአንቺ ወንዱንና ሴቱን እሰባብራለሁ፤በአንቺ ሽማግሌውንና ወጣቱን እሰባብራለሁ።በአንቺ ጐረምሳውንና ኰረዳዪቱን እሰባብራለሁ።

23 በአንቺ እረኛውንና መንጋውን እሰባብራለሁ፣በአንቺ ገበሬውንና በሬውን እሰባብራለሁ፤በአንቺ ገዦችንና ባለ ሥልጣኖችን እሰባብራለሁ።

24 “በጽዮን ላይ ስላደረሱት ጥፋት ሁሉ ለባቢሎንና በባቢሎን ለሚኖሩት ሁሉ ዐይናችሁ እያየ ዋጋቸውን እከፍላቸዋለሁ” ይላል እግዚአብሔር።

25 “አንቺ ምድርን ሁሉ ያጠፋሽ፣አጥፊ ተራራ ሆይ፤ እኔ በአንቺ ላይ ነኝ፣”ይላል እግዚአብሔር፤“እጄን በአንቺ ላይ አነሣለሁ፤ከገመገም ቍልቍል አንከባልልሻለሁ፤የተቃጠለም ተራራ አደርግሻለሁ።

26 ከአንቺ ለማእዘን የሚሆን ድንጋይ፣ለመሠረትም የሚሆን ዐለት አይወሰድም፤ለዘላለም ባድማ ትሆኛለሽ፤”ይላል እግዚአብሔር።

27 “በምድር ሁሉ ላይ ሰንደቅ ዐላማ አንሡ!በሕዝቦች መካከል መለከትን ንፉ!ሕዝቦችን ለጦርነት በእርሷ ላይ አዘጋጁ፤የአራራትን፣ የሚኒንና የአስከናዝን መንግሥታት፣ጠርታችሁ በእርሷ ሰብስቡአቸው፤የጦር አዝማች ሹሙባት፤ፈረሶችንም እንደ አንበጣ መንጋ ስደዱባት።