ኤርምያስ 51:54-60 NASV

54 “ከባቢሎን ጩኸት፣ከባቢሎናውያንምየ ምድር፣የታላቅ ጥፋት ድምፅ ይሰማል።

55 እግዚአብሔር ባቢሎንን ያጠፋታል፤ታላቅ ጩኸቷንም ጸጥ ያደርጋል።ሞገዳቸው እንደ ታላቅ ውሃ ይተማል፤ጩኸታቸውም ያስተጋባል።

56 በባቢሎን ላይ አጥፊ ይመጣል፤ጦረኞቿ ይማረካሉ፤ቀስታቸውም ይሰበራል፤ እግዚአብሔር ግፍን የሚበቀል፣ተገቢውንም ሁሉ የሚከፍል አምላክ ነውና።

57 ባለ ሥልጣኖቿንና ጥበበኞቿን፣ገዦቿንና መኳንንቷን፣ ጦረኞቿንም አሰክራለሁ፤ለዘላለም ይተኛሉ፤ አይነቁምም፤”ይላል ስሙ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር የሆነው ንጉሥ።

58 የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ወፍራሙ የባቢሎን ቅጥር ፈጽሞ ይፈርሳል፤ከፍ ያሉት ደጆቿም በእሳት ይቃጠላሉ፤ሰዎቹ በከንቱ ይደክማሉ፤የሕዝቡም ልፋት ለእሳት ይሆናል።”

59 የይሁዳ ንጉሥ ሴዴቅያስ በነገሠ በአራተኛው ዓመት፣ የንጉሡ የግቢ አስከልካይ የነበረው የመሕሤያ ልጅ የኔርያ ልጅ ሠራያ ከንጉሡ ጋር ወደ ባቢሎን በሄደ ጊዜ፣ ነቢዩ ኤርምያስ የሰጠው መልእክት ይህ ነው።

60 ኤርምያስ ስለ ባቢሎን ጽፎ ያስቀመጠውን ሁሉ፣ በባቢሎን ላይ የሚመጣውን ጥፋት ሁሉ በብራና ጥቅልል ላይ ጻፈው፤