1 በዐሥራ ሁለተኛው ዓመት፣ በዐሥራ ሁለተኛው ወር፣ በመጀመሪያው ቀን የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤
2 “የሰው ልጅ ሆይ፤ ለግብፅ ንጉሥ ለፈርዖን ሙሾ አውርድ፤ እንዲህም በለው፤“ ‘አንተ በሕዝቦች መካከል እንደ አንበሳ፣በባሕሮችም ውስጥ እንደ አስፈሪ አውሬ ነህ፤በወንዞችህ የምትንቦጫረቅ፣ውሃውን በእግርህ የምትመታ፣ምንጮችን የምታደፈርስ ነህ።
3 “ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ ‘ብዙ ሕዝብ ይዤ፣መረቤን በላይህ ላይ እጥላለሁ፤በመረቤም ጐትተው ያወጡሃል።
4 በምድር ላይ እጥልሃለሁ፤ሜዳም ላይ እዘረጋሃለሁ፤የሰማይ ወፎች ሁሉ እንዲሰፍሩብህ አደርጋለሁ፤የምድር አራዊት ሁሉ በመስገብገብ ይበሉሃል።
5 ሥጋህን በተራሮች ላይ እበታትነዋለሁ፤የተረፈውንም በየሸለቆው እሞላዋለሁ።
6 እስከ ተራሮች ባለው መንገድ ሁሉ፣በሚፈሰው ደምህ ምድሪቱን አርሳታለሁ፤ሸለቆዎችም በሥጋህ ይሞላሉ።
7 አንተን በማጠፋ ጊዜ ሰማያትን እሸፍናለሁ፤ከዋክብታቸውንም አጨልማለሁ፤ፀሓይን በደመና እሸፍናለሁ፤ጨረቃም ብርሃኗን አትሰጥም።