ኢሳይያስ 65:18-24 NASV

18 ነገር ግን በምፈጥረው፣ደስ ይበላችሁ፤ ለዘላለም ሐሤት አድርጉ።ኢየሩሳሌምን ለደስታ፣ሕዝቧን ለሐሤት እፈጥራለሁና።

19 በኢየሩሳሌም እደሰታለሁ፤በሕዝቤ ሐሤት አደርጋለሁ፤የልቅሶና የጩኸት ድምፅ፣ከእንግዲህ በዚያ አይሰማም።

20 “ከእንግዲህም በዚያ፣ለጥቂት ጊዜ ብቻ በሕይወት የሚኖር ሕፃን፣ወይም ዕድሜ ያልጠገበ አረጋዊ አይኖርም፤አንድ መቶ ዓመት የሞላው ሰው ቢሞት፣በአጭር እንደ ተቀጨ ይቈጠራል፤አንድ ሰው መቶ ዓመት ሳይሞላው ቢሞት፣እንደ ተቀሠፈ ይገመታል።

21 ሰዎች ቤት ይሠራሉ፤ በውስጡም ይኖራሉ፤ወይንን ይተክላሉ፤ ፍሬውንም ይበላሉ።

22 ከእንግዲህ ለሌሎች መኖሪያ ቤት አይሠሩም፤ወይም ሌላው እንዲ በላው አይተክሉም፤የሕዝቤ ዕድሜ፣እንደ ዛፍ ዕድሜ ይረዝማል፤እኔ የመረጥኋቸው፣በእጃቸው ሥራ ለረጅም ዘመን ደስ ይላቸዋል።

23 ድካማቸው በከንቱ አይቀርም፤ዕድለ ቢስ ልጆችም አይወልዱም፤እነርሱና ዘራቸው፣ እግዚአብሔር የባረከው ሕዝብ ይሆናሉ።

24 ገና ሳይጣሩ እመልስላቸዋለሁ፤ተናግረው ሳይጨርሱ እሰማለሁ።