ኤርምያስ 15:9-15 NASV

9 የሰባቶቹ እናት ትዝለፈለፋለች፤ትንፋሿም ይጠፋል፤ገና ቀን ሳለ ፀሓይዋ ትጠልቃለች፤እርሷም ታፍራለች፤ ትዋረዳለችም፤የተረፉትንም በጠላቶቻቸው ፊት፣ለሰይፍ እዳርጋቸዋለሁ፤”ይላል እግዚአብሔር።

10 ወይኔ እናቴ! ለምድር ሁሉ፣የጭቅጭቅና የክርክር ሰው የሆንሁትን ምነው ወለድሽ!ለማንም አላበደርሁም፤ ከማንም አልተበደርሁም፤ነገር ግን ሰው ሁሉ ይረግመኛል።

11 እግዚአብሔር እንዲህ አለ፤“በእርግጥ ለበጎ ዐላማ እታደግሃለሁ፤በመከራና በጭንቅ ጊዜም፣ጠላቶችህ ደጅ እንዲጠኑህ በእውነት አደርጋለሁ።

12 “ሰው ብረትን፣ ከሰሜን የመጣን ብረት፣ነሐስንስ መስበር ይችላልን?

13 በመላ አገርህ፣ስላለው ኀጢአትህ ሁሉ፣ሀብትና ንብረትህን፣ያለ ዋጋ አሳልፌ ለምርኮ እሰጣለሁ።

14 ቍጣዬ በላያችሁ፣የሚነድ እሳት ትጭራለችና፣በማታውቀው አገር፣ለጠላቶችህ ባሪያ አደርግሃለሁ።”

15 እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ታውቃለህ፤እንግዲህ አስበኝ፤ ጐብኘኝም፤አሳዳጆቼን ተበቀልልኝ።ታጋሽ እንደ መሆንህ አታጥፋኝ፤ባንተ ምክንያት የሚደርስብኝን ነቀፋ አስብ።