4 የያዕቆብ ቤት ሆይ፤ የእስራኤል ቤት ወገን ሁላችሁ፣ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ።
5 እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“አባቶቻችሁ ከእኔ የራቁት፣ከንቱ ነገርን የተከተሉት፣ራሳቸውም ከንቱ የሆኑት፣ምን ጥፋት አግኝተውብኝ ነው?
6 እነርሱም፣ ‘ከግብፅ ምድር ያወጣን፣በወና ምድረ በዳ፣በጐድጓዳና በበረሓ መሬት፣በደረቅና በጨለማ ቦታ፣ሰው በማያልፍበትና በማይኖርበት ስፍራ፣የመራን እግዚአብሔር ወዴት ነው?’ ብለው አልጠየቁም።
7 እኔ፣ ፍሬዋንና በረከቷን እንድትበሉ፣ለም ወደ ሆነ መሬት አመጣኋችሁ፤እናንተ ግን መጥታችሁ ምድሬን አረከሳችሁ፤ርስቴንም ጸያፍ አደረጋችሁ።
8 ‘እግዚአብሔር ወዴት ነው?’ ብለው፣ካህናቱ አልጠየቁም፤ከሕጉ ጋር የሚውሉት አላወቁኝም፤መሪዎቹ ዐመፁብኝ፤ነቢያቱም በበኣል ስም ተነበዩ፤ከንቱ ነገሮችን ተከተሉ።
9 “ስለዚህ እንደ ገና ከእናንተ ጋር እፋረዳለሁ፤”“ከልጅ ልጆቻችሁም ጋር እከራከራለሁ።ይላል እግዚአብሔር።
10 ወደ ኪቲም ጠረፍ ተሻገሩና እዩ፤ወደ ቄዳርም ልካችሁ በጥንቃቄ መርምሩ፣እንዲህ ዐይነት ነገር ተደርጎ ያውቅ እንደሆነ ተመልከቱ፤