ኤርምያስ 2:6-12 NASV

6 እነርሱም፣ ‘ከግብፅ ምድር ያወጣን፣በወና ምድረ በዳ፣በጐድጓዳና በበረሓ መሬት፣በደረቅና በጨለማ ቦታ፣ሰው በማያልፍበትና በማይኖርበት ስፍራ፣የመራን እግዚአብሔር ወዴት ነው?’ ብለው አልጠየቁም።

7 እኔ፣ ፍሬዋንና በረከቷን እንድትበሉ፣ለም ወደ ሆነ መሬት አመጣኋችሁ፤እናንተ ግን መጥታችሁ ምድሬን አረከሳችሁ፤ርስቴንም ጸያፍ አደረጋችሁ።

8 ‘እግዚአብሔር ወዴት ነው?’ ብለው፣ካህናቱ አልጠየቁም፤ከሕጉ ጋር የሚውሉት አላወቁኝም፤መሪዎቹ ዐመፁብኝ፤ነቢያቱም በበኣል ስም ተነበዩ፤ከንቱ ነገሮችን ተከተሉ።

9 “ስለዚህ እንደ ገና ከእናንተ ጋር እፋረዳለሁ፤”“ከልጅ ልጆቻችሁም ጋር እከራከራለሁ።ይላል እግዚአብሔር።

10 ወደ ኪቲም ጠረፍ ተሻገሩና እዩ፤ወደ ቄዳርም ልካችሁ በጥንቃቄ መርምሩ፣እንዲህ ዐይነት ነገር ተደርጎ ያውቅ እንደሆነ ተመልከቱ፤

11 የእውነት አማልክት ባይሆኑም እንኳ፣አማልክቱን የለወጠ ሕዝብ አለን?ሕዝቤ ግን ክብራቸውሠ የሆነውን፣በከንቱ ነገር ለወጡ።

12 ሰማያት ሆይ፤ በዚህ ተገረሙ፤በታላቅ ድንጋጤም ተንቀጥቀጡ፤”ይላል እግዚአብሔር።