ኤርምያስ 3:9-15 NASV

9 በቅሌቷም ምድሪቱን አረከሰች፤ ከድንጋይና ከግንድ ጋር አመነዘረች፤

10 ይህም ሁሉ ሆኖ ከሓዲዋ እኅቷ ይሁዳ ወደ እኔ የተመለሰችው በማስመሰል እንጂ በሙሉ ልቧ አልነበረም” ይላል እግዚአብሔር።

11 እግዚአብሔር እንዲህ አለኝ፤ “ከከሓዲዋ ይሁዳ ይልቅ ከዳተኛዪቱ እስራኤል ጻድቅ ሆና ተገኘች።

12 ሂድና ይህን መልእክት ወደ ሰሜን እንዲህ ብለህ ተናገር፤“ ‘ከዳተኛዪቱ እስራኤል ሆይ፤ ተመለሽ’ ይላል እግዚአብሔር፤‘እኔ መሓሪ ስለ ሆንሁ፣ከእንግዲህ በቍጣ ዐይን አላይሽም’ይላል እግዚአብሔር። ‘ለዘላለም አልቈጣም።

13 በአምላክሽ በእግዚአብሔር ላይ በማመፅሽ፣ክብርሽንም ለእንግዶች አማልክት፣በየለምለሙ ዛፍ ሥር አሳልፈሽ በመስጠት፣ለእኔ ባለመታዘዝሽ፣በደለኛ መሆንሽን ይህን አንድ ነገር ብቻ እመኚ’ ”ይላል እግዚአብሔር።

14 “ከዳተኛ ልጆች ሆይ፤ እኔ ባለቤታችሁ ነኝና ተመለሱ” ይላል እግዚአብሔር፤ “ከአንድ ከተማ አንድ፣ ከአንድ ነገድ ሁለት መርጫችሁ ወደ ጽዮን አመጣችኋለሁ።

15 እንደ ልቤም የሆኑ፣ በዕውቀትና በማስተዋል የሚመሯችሁን እረኞች እሰጣችኋለሁ።