ኤርምያስ 5:13-19 NASV

13 ነቢያቱ ነፋስ እንጂ ሌላ ነገር አይደሉም፤ቃሉም በውስጣቸው የለም፤ያሉት ሁሉ በእነርሱ ላይ ይመለስ።”

14 ስለዚህ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ሕዝቡ ይህን ቃል ስለ ተናገረ፣ቃሌን በአፍህ ውስጥ የሚፋጅ እሳት፣ይህንም ሕዝብ ማገዶ አደርጋለሁ፤እሳቱም ይበላቸዋል።

15 የእስራኤል ቤት ሆይ፣” ይላል እግዚአብሔር፤“ከሩቅ ሕዝብን አመጣባችኋለሁ፤ጥንታዊና ብርቱ፣ቋንቋውን የማታውቁት፣ ንግግሩንምየማትረዱት ሕዝብ ነው።

16 የፍላጻቸው ሰገባ እንደ ተከፈተ መቃብር ነው፤ሁሉም ብርቱ ተዋጊዎች ናቸው።

17 ሰብልህንና ምግብህን ጠራርገው ይበሉብሃል፤ወንዶችና ሴቶች ልጆችህን ይውጣሉ፣በጎችህንና ከብቶችህን ይፈጃሉ፤የወይን ተክሎችህንና የበለስ ዛፎችህን ያወድማሉ፤የታመንህባቸውንም የተመሸጉ ከተሞች፣በሰይፍ ያጠፉአቸዋል።

18 “ይሁን እንጂ፣ በዚያን ዘመን እንኳ” ይላል እግዚአብሔር፤ “ፈጽሜ አላጠፋችሁም።

19 ሕዝቡ፣ ‘እግዚአብሔር አምላካችን ይህን ሁሉ ነገር ለምን አደረገብን?’ ብለው ቢጠይቁ ‘እኔን፣ እንደ ተዋችሁኝና በራሳችሁ ምድር ባዕዳን አማልክትን እንዳገለገላችሁ፣ እንደዚሁ የእናንተ ባልሆነ ምድር ባዕዳንን ታገለግላላችሁ’ ትላቸዋለህ።