9 ስለ እነዚህ ነገሮች አልቀጣቸውምን?”ይላል እግዚአብሔር።“እኔ ራሴ እንደዚህ ዐይነቱን ሕዝብ፣አልበቀልምን?
10 “ወደ ወይን አትክልቷ ስፍራ ገብታችሁ አበላሹት፤ነገር ግን ፈጽማችሁ አታጥፉት፤ቅርንጫፎቿን ገነጣጥሉ፤ የእግዚአብሔር አይደሉምና፤
11 የእስራኤል ቤትና የይሁዳ ቤት፣ፈጽመው ከድተውኛል፤”ይላል እግዚአብሔር።
12 በእግዚአብሔር ላይ ሐሰትን ተናገሩ፤እንዲህም አሉ፤ “እሱ ምንም አያደርግም!ክፉ ነገር አይደርስብንም፤ሰይፍም ራብም አናይም፤
13 ነቢያቱ ነፋስ እንጂ ሌላ ነገር አይደሉም፤ቃሉም በውስጣቸው የለም፤ያሉት ሁሉ በእነርሱ ላይ ይመለስ።”
14 ስለዚህ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ሕዝቡ ይህን ቃል ስለ ተናገረ፣ቃሌን በአፍህ ውስጥ የሚፋጅ እሳት፣ይህንም ሕዝብ ማገዶ አደርጋለሁ፤እሳቱም ይበላቸዋል።
15 የእስራኤል ቤት ሆይ፣” ይላል እግዚአብሔር፤“ከሩቅ ሕዝብን አመጣባችኋለሁ፤ጥንታዊና ብርቱ፣ቋንቋውን የማታውቁት፣ ንግግሩንምየማትረዱት ሕዝብ ነው።