ኤርምያስ 14:12-18 NASV

12 ቢጾሙም ጩኸታቸውን አልሰማም፤ የሚቃጠል መሥዋዕትና የእህል ቍርባን ቢያቀርቡም አልቀበላቸውም፤ ነገር ግን በሰይፍ፣ በራብና በቸነፈር አጠፋቸዋለሁ።”

13 እኔም፣ “ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፤ ወዮ!፣ ነቢያቱ ‘ሰይፍ አታዩም፤ ራብም አያገኛችሁም፤ ነገር ግን በዚህ ስፍራ ዘለቄታ ያለው ሰላም እሰጣችኋለሁ’ ይላል ይሏቸዋል” አልሁ።

14 እግዚአብሔርም እንዲህ አለኝ፤ “ነቢያቱ በስሜ የሐሰት ትንቢት ይናገራሉ፤ እኔ አልላክኋቸውም፤ አላዘዝኋቸውም፤ አልተናገርኋቸውምም። የሐሰት ራእይ፣ ሟርት፣ ከንቱ ነገርንና የልባቸውን ሽንገላ ይተነብዩላችኋል።

15 ስለዚህ በስሜ የሐሰት ትንቢት ስለሚናገሩ ነቢያት እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ እኔ ሳልልካቸው፣ ‘ሰይፍና ራብ በዚች ምድር ላይ አይመጣም’ የሚሉ እነዚህ ነቢያት በሰይፍና በራብ ይጠፋሉ፤

16 ትንቢቱ የተነገረለትም ሕዝብ ከሰይፍና ከራብ የተነሣ በኢየሩሳሌም አደባባዮች ይወድቃል፤ እነርሱንም ሆነ ሚስቶቻቸውን ወይም ወንዶችና ሴቶች ልጆቻቸውን የሚቀብራቸው አይገኝም። ለበደላቸው የሚገባውንም ቅጣት በላያቸው አወርዳለሁ።

17 “ይህን ቃል እንዲህ ብለህ ንገራቸው፤“ ‘ድንግሊቱ ልጄ፣ ሕዝቤ፣በታላቅ ስብራት፣በብርቱ ቍስል ተመትታለችናዐይኖቼ ቀንና ሌሊት፣ ሳያቋርጡእንባ ያፈስሳሉ

18 ወደ ገጠር ብወጣ፣በሰይፍ የተገደሉትን አያለሁ፤ወደ ከተማ ብገባ፣ በራብ የወደቁትን አያለሁነቢዩም ካህኑም፣ወደማያውቁት አገር ሸሽተዋል።’ ”