ኤርምያስ 5:2-8 NASV

2 ‘ሕያው እግዚአብሔርን! ቢሉም፣የሚምሉት በሐሰት ነው።”

3 እግዚአብሔር ሆይ፤ ዐይኖችህ እውነትን አይመለከቱምን?አንተ መታሃቸው፤ እነርሱ ግን አልተሰማቸውም፤አደቀቅሃቸው፤ እነርሱ ግን አልታረሙም፤ፊታቸውን ከድንጋይ ይልቅ አጠነከሩበንስሓ ለመመለስም አልፈለጉም።

4 እኔም በልቤ እንዲህ አልሁ፤ “እነዚህ ድኾች ናቸው፤ሞኞች ናቸው፤ የእግዚአብሔርን መንገድ፣የአምላካቸውን ሕግ አላወቁምና።

5 ስለዚህ ወደ ታላላቆቹ እሄዳለሁ፤ለእነርሱም እናገራለሁ፤በእርግጥ እነርሱ የእግዚአብሔርን መንገድ፣የአምላካቸውንም ሕግ ያውቃሉና።”ነገር ግን እነርሱም ቢሆኑ ያው እንደዚያው ቀንበሩን ሰብረዋል፤እስራቱንም በጥሰዋል።

6 ስለዚህ አንበሳ ከዱር ወጥቶ ይሰባብራቸዋል፣የበረሓ ተኵላም ይቦጫጭቃቸዋል፤ብቅ የሚለውን ሰው ሁሉ ለመገነጣጠል፣ነብር በከተሞቻቸው ዙሪያ ያደባል፤ዐመፃቸው ታላቅ፣ክሕደታቸው ብዙ ነውና።

7 “ታዲያ፣ እንዴት ይቅር ልልሽ እችላለሁ?ልጆችሽ ትተውኛል፤እውነተኛውን አምላክ ትተው አማልክት ባልሆኑት ምለዋል፤እስኪጠግቡ ድረስ መገብኋቸው፤እነርሱ ግን አመነዘሩ፤ወደ ጋለሞቶችም ቤት ተንጋጉ።

8 እንደ ተቀለበ ብርቱ ድንጒላ ፈረስ ሆኑ፤እያንዳንዱም የሌላውን ሚስት ተከትሎ አሽካካ።