ኤርምያስ 5:5-11 NASV

5 ስለዚህ ወደ ታላላቆቹ እሄዳለሁ፤ለእነርሱም እናገራለሁ፤በእርግጥ እነርሱ የእግዚአብሔርን መንገድ፣የአምላካቸውንም ሕግ ያውቃሉና።”ነገር ግን እነርሱም ቢሆኑ ያው እንደዚያው ቀንበሩን ሰብረዋል፤እስራቱንም በጥሰዋል።

6 ስለዚህ አንበሳ ከዱር ወጥቶ ይሰባብራቸዋል፣የበረሓ ተኵላም ይቦጫጭቃቸዋል፤ብቅ የሚለውን ሰው ሁሉ ለመገነጣጠል፣ነብር በከተሞቻቸው ዙሪያ ያደባል፤ዐመፃቸው ታላቅ፣ክሕደታቸው ብዙ ነውና።

7 “ታዲያ፣ እንዴት ይቅር ልልሽ እችላለሁ?ልጆችሽ ትተውኛል፤እውነተኛውን አምላክ ትተው አማልክት ባልሆኑት ምለዋል፤እስኪጠግቡ ድረስ መገብኋቸው፤እነርሱ ግን አመነዘሩ፤ወደ ጋለሞቶችም ቤት ተንጋጉ።

8 እንደ ተቀለበ ብርቱ ድንጒላ ፈረስ ሆኑ፤እያንዳንዱም የሌላውን ሚስት ተከትሎ አሽካካ።

9 ስለ እነዚህ ነገሮች አልቀጣቸውምን?”ይላል እግዚአብሔር።“እኔ ራሴ እንደዚህ ዐይነቱን ሕዝብ፣አልበቀልምን?

10 “ወደ ወይን አትክልቷ ስፍራ ገብታችሁ አበላሹት፤ነገር ግን ፈጽማችሁ አታጥፉት፤ቅርንጫፎቿን ገነጣጥሉ፤ የእግዚአብሔር አይደሉምና፤

11 የእስራኤል ቤትና የይሁዳ ቤት፣ፈጽመው ከድተውኛል፤”ይላል እግዚአብሔር።