ኤርምያስ 50:33-39 NASV

33 የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“የእስራኤል ሕዝብና የይሁዳ ሕዝብ፣በአንድነት ተጨቍነዋል፤የማረኳቸውም ሁሉ አጥብቀው ይዘዋቸዋል፤ይለቅቋቸውም ዘንድ እንቢ ብለዋል።

34 ነገር ግን ቤዛቸው ብርቱ ነው፤ስሙም የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ነው፤ለምድራቸው ዕረፍትን ለመስጠት፤ተግቶ ይሟገትላቸዋል፤በባቢሎን የሚኖሩትን ግን ዕረፍት ይነሣቸዋል።

35 “ሰይፍ በባቢሎናውያን ላይ መጣ!”ይላል እግዚአብሔር፤“በባቢሎን ነዋሪዎች ላይ፤በባለ ሥልጣኖቿና በጥበበኞቿም ላይ ተመዘዘ!

36 ሰይፍ በሐሰተኞች ነቢያቷ ላይ መጣ!እነርሱም ሞኞች ይሆናሉ፤ሰይፍ በጦረኞቿ ላይ ተመዘዘ፤እነርሱም ይሸበራሉ።

37 ሰይፍ በፈረሰኞቿና በሠረገሎቿ ላይ፣በመካከሏ ባሉት ባዕዳን ወታደሮች ሁሉ ላይ መጣ!እነርሱም እንደ ሴቶች ይሆናሉ፤ሰይፍ በሀብት ንብረቷ ላይ መጣ!ለዝርፊያም ይሆናሉ።

38 ድርቅ በውሆቿ ላይ መጣ!እነሆ፤ ይደርቃሉ፤ምድሪቱ በፍርሀት በሚሸበሩ አማልክት፣በጣዖትም ብዛት ተሞልታለችና።

39 “ስለዚህ የምድረ በዳ አራዊትና የጅብ መኖሪያ፣የጒጒትም ማደሪያ ትሆናለች፤ከእንግዲህ ወዲህ ማንም አይኖርባትም፤ከትውልድ እስከ ትውልድም የሚቀመጥባት አይገኝም።