ኤርምያስ 14:14-20 NASV

14 እግዚአብሔርም እንዲህ አለኝ፤ “ነቢያቱ በስሜ የሐሰት ትንቢት ይናገራሉ፤ እኔ አልላክኋቸውም፤ አላዘዝኋቸውም፤ አልተናገርኋቸውምም። የሐሰት ራእይ፣ ሟርት፣ ከንቱ ነገርንና የልባቸውን ሽንገላ ይተነብዩላችኋል።

15 ስለዚህ በስሜ የሐሰት ትንቢት ስለሚናገሩ ነቢያት እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ እኔ ሳልልካቸው፣ ‘ሰይፍና ራብ በዚች ምድር ላይ አይመጣም’ የሚሉ እነዚህ ነቢያት በሰይፍና በራብ ይጠፋሉ፤

16 ትንቢቱ የተነገረለትም ሕዝብ ከሰይፍና ከራብ የተነሣ በኢየሩሳሌም አደባባዮች ይወድቃል፤ እነርሱንም ሆነ ሚስቶቻቸውን ወይም ወንዶችና ሴቶች ልጆቻቸውን የሚቀብራቸው አይገኝም። ለበደላቸው የሚገባውንም ቅጣት በላያቸው አወርዳለሁ።

17 “ይህን ቃል እንዲህ ብለህ ንገራቸው፤“ ‘ድንግሊቱ ልጄ፣ ሕዝቤ፣በታላቅ ስብራት፣በብርቱ ቍስል ተመትታለችናዐይኖቼ ቀንና ሌሊት፣ ሳያቋርጡእንባ ያፈስሳሉ

18 ወደ ገጠር ብወጣ፣በሰይፍ የተገደሉትን አያለሁ፤ወደ ከተማ ብገባ፣ በራብ የወደቁትን አያለሁነቢዩም ካህኑም፣ወደማያውቁት አገር ሸሽተዋል።’ ”

19 ይሁዳን ፈጽመህ ጥለኸዋልን?ነፍስህስ ጽዮንን ተጸየፈቻትን?ፈውስ እስከማይገኝልን ድረስ፣ለምን ክፉኛ መታኸን?ሰላምን ተስፋ አደረግን፤ሆኖም በጎ ነገር አላገኘንም፤የፈውስን ጊዜ ተጠባበቅን፤ነገር ግን ሽብር ብቻ ሆነ።

20 እግዚአብሔር ሆይ፤ ክፋታችንን ዐውቀናልና፤የአባቶቻችንን በደል ተረድተናልና፤በእርግጥም በአንተ ላይ ኀጢአት ሠርተናል።