ኤርምያስ 51:7-13 NASV

7 ባቢሎን በእግዚአብሔር እጅ የወርቅ ጽዋ ነበረች፤ምድርንም ሁሉ አሰከረች።ሕዝቦች ከወይን ጠጇ ጠጡ፤ስለዚህ አሁን አብደዋል።

8 ባቢሎን በድንገት ወድቃ ትሰበራለች፤ዋይ በሉላት!ምናልባት ልትፈወስ ስለምትችል፣ለቍስሏ የሚቀባ መድኀኒት ፈልጉላት።

9 “ ‘ባቢሎንን ለመፈወስ ሞክረን ነበር፤እርሷ ግን ልትፈወስ አትችልም፤ፍርዷ እስከ ሰማይ ስለ ደረሰ፣እስከ ደመናም ድረስ ከፍ ስላለ፣ትተናት ወደየአገራችን እንሂድ።’

10 “ ‘እግዚአብሔር ቅንነታችንን መሰከረ፤ኑ፤ አምላካችን እግዚአብሔር ያደረገውን፣በጽዮን እንናገር።’

11 “ፍላጾችን ሳሉ፤ጋሻዎችን አዘጋጁ፤ የእግዚአብሔር ሐሳብ ባቢሎንን ለማጥፋት ስለ ሆነ፣የሜዶንን ነገሥታት አነሣሥቶአል፤ እግዚአብሔር ይበቀላል፤ስለ ቤተ መቅደሱ ይበቀላል።

12 በባቢሎን ቅጥር ላይ ዐላማ አንሡጥበቃውን አጠናክሩ፤ዘብ ጠባቂዎችን አቁሙ፤ደፈጣ ተዋጊዎችን አዘጋጁ እግዚአብሔር በባቢሎን ሕዝብ ላይ የወሰነውን፣ዐላማውን ያከናውናል።

13 አንቺ በብዙ ውሃ አጠገብ የምትኖሪ፣በሀብትም የበለጸግሽ ሆይ፤የምትወገጂበት ጊዜ ወጥቶአል፤ፍጻሜሽ ደርሶአል።