132 ስምህን ለሚወዱ ማድረግ ልማድህ እንደሆነ ሁሉ፣ወደ እኔ ተመልሰህ፣ ምሕረት አድርግልኝ።
133 አካሄዴን እንደ ቃልህ ቀና አድርግልኝ፤ኀጢአትም በላዬ እንዲሠለጥን አትፍቀድ።
134 ትእዛዝህን መጠበቅ እንድችል፣ከሰዎች ጥቃት ታደገኝ።
135 በባሪያህ ላይ ፊትህን አብራ፤ሥርዐትህንም አስተምረኝ።
136 ሕግህ ባለመከበሩ፤እንባዬ እንደ ውሃ ይፈሳል።
137 እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ጻድቅ ነህ፤ፍርድህም ትክክል ነው።
138 ምስክርነትህን በጽድቅ አዘዝህ፤እጅግ አስተማማኝም ነው።