መዝሙር 29 NASV

ለማዕበሉ ጌታ የቀረበ ውዳሴ

የዳዊት መዝሙር

1 እናንተ ኀያላን፣ ለእግዚአብሔር ስጡ፤ክብርንና ብርታትን ለእግዚአብሔር ስጡ።

2 ለስሙ የሚገባ ክብር ለእግዚአብሔር ስጡ፤በቅድስናው ግርማ ለእግዚአብሔር ስገዱ።

3 የእግዚአብሔር ድምፅ በውሆች ላይ ነው፤የክብር አምላክ አንጐደጐደ፤ እግዚአብሔር በታላላቅ ውሆች ላይ አንጐደጐደ።

4 የእግዚአብሔር ድምፅ ኀያል ነው፤ የእግዚአብሔር ድምፅ ግርማዊ ነው።

5 የእግዚአብሔር ድምፅ ዝግባን ይሰብራል፤ እግዚአብሔር የሊባኖስን ዝግባ ይሰባብራል።

6 ሊባኖስን እንደ ጥጃ፣ስርዮንንም እንደ አውራሪስ ግልገል ያዘልላል።

7 የእግዚአብሔር ድምፅየእሳት ነበልባል ይረጫል።

8 የእግዚአብሔር ድምፅ ምድረ በዳውን ያናውጣል፤ የእግዚአብሔር ድምፅ የቃዴስን ምድረ በዳ ያናውጣል።

9 የእግዚአብሔር ድምፅ ወርካዎችን ይወዘውዛል፤ጫካዎችንም ይመነጥራል፤ሁሉም በእርሱ ቤተ መቅደስ ሆኖ “ይክበር!” ይላል።

10 እግዚአብሔር በጐርፍ ላይ ዙፋኑን ዘርግቶ ተቀምጦአል፤ እግዚአብሔር በንጉሥነቱ ለዘላለም በዙፋኑ ላይ ይቀመጣል።

11 እግዚአብሔር ለሕዝቡ ብርታትን ይሰጣል፤ እግዚአብሔር ሕዝቡን በሰላም ይባርካል።