መዝሙር
ምዕራፎች 29
መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም
ለማዕበሉ ጌታ የቀረበ ውዳሴ
የዳዊት መዝሙር
1እናንተ ኀያላን፣ ለእግዚአብሔር ስጡ፤ክብርንና ብርታትን ለእግዚአብሔር ስጡ። 2ለስሙ የሚገባ ክብር ለእግዚአብሔር ስጡ፤በቅድስናው ግርማ ለእግዚአብሔር ስገዱ። 3 የእግዚአብሔር ድምፅ በውሆች ላይ ነው፤የክብር አምላክ አንጐደጐደ፤ እግዚአብሔር በታላላቅ ውሆች ላይ አንጐደጐደ። 4 የእግዚአብሔር ድምፅ ኀያል ነው፤ የእግዚአብሔር ድምፅ ግርማዊ ነው። 5 የእግዚአብሔር ድምፅ ዝግባን ይሰብራል፤ እግዚአብሔር የሊባኖስን ዝግባ ይሰባብራል። 6ሊባኖስን እንደ ጥጃ፣ስርዮንንም እንደ አውራሪስ ግልገል ያዘልላል። 7 የእግዚአብሔር ድምፅየእሳት ነበልባል ይረጫል። 8 የእግዚአብሔር ድምፅ ምድረ በዳውን ያናውጣል፤ የእግዚአብሔር ድምፅ የቃዴስን ምድረ በዳ ያናውጣል። 9 የእግዚአብሔር ድምፅ ወርካዎችን ይወዘውዛል፤ጫካዎችንም ይመነጥራል፤ሁሉም በእርሱ ቤተ መቅደስ ሆኖ “ይክበር!” ይላል። 10 እግዚአብሔር በጐርፍ ላይ ዙፋኑን ዘርግቶ ተቀምጦአል፤ እግዚአብሔር በንጉሥነቱ ለዘላለም በዙፋኑ ላይ ይቀመጣል። 11 እግዚአብሔር ለሕዝቡ ብርታትን ይሰጣል፤ እግዚአብሔር ሕዝቡን በሰላም ይባርካል።ምዕራፎች
1
2
3
4
5
6
7
8
9
10
11
12
13
14
15
16
17
18
19
20
21
22
23
24
25
26
27
28
29
30
31
32
33
34
35
36
37
38
39
40
41
42
43
44
45
46
47
48
49
50
51
52
53
54
55
56
57
58
59
60
61
62
63
64
65
66
67
68
69
70
71
72
73
74
75
76
77
78
79
80
81
82
83
84
85
86
87
88
89
90
91
92
93
94
95
96
97
98
99
100
101
102
103
104
105
106
107
108
109
110
111
112
113
114
115
116
117
118
119
120
121
122
123
124
125
126
127
128
129
130
131
132
133
134
135
136
137
138
139
140
141
142
143
144
145
146
147
148
149
150