መዝሙር
ምዕራፎች 84
መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም
ወደ መቅደሱ ጒዞ መዝሙር
ለመዘምራን አለቃ፤ በዋሽንት የሚዜም የቆሬ ልጆች መዝሙር
1የሰራዊት አምላክ ሆይ፤ማደሪያህ ምንኛ የተወደደ ነው! 2ነፍሴ የእግዚአብሔርን አደባባዮች ትናፍቃለች፤እጅግም ትጓጓለታለች፤ልቤና ሥጋዬም፣ለሕያው አምላክ እልል በሉ። 3ንጉሤና አምላኬ የሰራዊት አምላክ ሆይ፤መሠዊያህ ባለበት ስፍራ፣ድንቢጥ እንኳ መኖሪያ ቤት፣ዋኖስም ጫጩቶቿን የምታኖርበት ጐጆ አገኘች። 4በቤትህ የሚኖሩ የተባረኩ ናቸው፤እነርሱም ለዘላለም ያመሰግኑሃል። ሴላ 5አንተን ብርታታቸው ያደረጉ፣በልባቸው የጽዮንን መንገድ የሚያስቡ ቡሩካን ናቸው። 6በልቅሶ ሸለቆ በሚያልፉበት ጊዜ፣የምንጭ መፍለቂያ ቦታ ያደርጉታል፤የበልጒም ዝናብ ያረሰርሰዋል። 7ከኀይል ወደ ኀይል ይሸጋገራሉ፤እያንዳንዱም በጽዮን ባለው አምላክ ፊት ይቀርባል። 8የሰራዊት አምላክ ሆይ፤ ጸሎቴን ስማ፤የያዕቆብ አምላክ ሆይ አድምጠኝ። ሴላ 9አምላክ ሆይ፤ ጋሻችንን እይልን፤የቀባኸውንም ተመልከት። 10በሌላ ስፍራ ሺህ ቀን ከመኖር፣በአደባባይህ አንዲት ቀን መዋል ይሻላል፤በክፉዎች ድንኳን ከመቀመጥ ይልቅ፣በአምላኬ ቤት ደጅ መቆም እመርጣለሁ። 11 እግዚአብሔር አምላክ ፀሓይና ጋሻ ነውና፤ እግዚአብሔር ሞገስንና ክብርን ይሰጣል፤እግዚአብሔር በቅንነት የሚሄዱትን፣ መልካም ነገር አይነፍጋቸውም። 12የሰራዊት አምላክ ሆይ፤በአንተ የታመነ ሰው ቡሩክ ነው።ምዕራፎች
1
2
3
4
5
6
7
8
9
10
11
12
13
14
15
16
17
18
19
20
21
22
23
24
25
26
27
28
29
30
31
32
33
34
35
36
37
38
39
40
41
42
43
44
45
46
47
48
49
50
51
52
53
54
55
56
57
58
59
60
61
62
63
64
65
66
67
68
69
70
71
72
73
74
75
76
77
78
79
80
81
82
83
84
85
86
87
88
89
90
91
92
93
94
95
96
97
98
99
100
101
102
103
104
105
106
107
108
109
110
111
112
113
114
115
116
117
118
119
120
121
122
123
124
125
126
127
128
129
130
131
132
133
134
135
136
137
138
139
140
141
142
143
144
145
146
147
148
149
150