መዝሙር
ምዕራፎች 30
መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም
ከክፉ አደጋ የዳነ ሰው ምስጋና
ለቤተ መቅደሱ ምረቃ የተዘመረ፤ የዳዊት መዝሙር
1 እግዚአብሔር ሆይ፤ ከታች አንሥተኸኛልና፣ጠላቶቼም በላዬ እንዳይደሰቱ አድርገሃልና፣ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ። 2 እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤ ትረዳኝ ዘንድ ወደ አንተ ጮኽሁ፤አንተም ፈወስኸኝ። 3 እግዚአብሔር ሆይ ነፍሴን ከሲኦል አወጣሃት፤ወደ ጒድጓድ ከመውረድም መልሰህ ሕያው አደረግኸኝ። 4እናንተ ቅዱሳኑ፤ ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤ቅዱስ ስሙንም አወድሱ። 5ቊጣው ለዐጭር ጊዜ ነው፤ቸርነቱ ግን እስከ ዕድሜ ልክ ነውና፤ሌሊቱን በልቅሶ ቢታደርም፣በማለዳ ደስታ ይመጣል። 6እኔም በተረጋጋሁ ጊዜ፣“ከቶ አልናወጥም” አልሁ። 7 እግዚአብሔር ሆይ፤ በአንተ ሞገስ፣ተራሮቼ ጸኑ፣ፊትህን በሰወርህ ጊዜ ግን፣ውስጤ ታወከ። 8 እግዚአብሔር ሆይ፤ ወደ አንተ ተጣራሁ፤ወደ ጌታም እንዲህ ብዬ ጮኽሁ፤ 9“በእኔ ወደ ጒድጓድ መውረድ፣በመሞቴ ምን ጥቅም ይገኛል?ዐፈር ያመሰግንሃልን?ታማኝነትህንስ ይናገራልን? 10 እግዚአብሔር ሆይ፤ ስማ፤ ማረኝም፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ ረዳት ሁነኝ።” 11ዋይታዬን ወደ ሽብሸባ ለወጥህልኝ፤ማቄን አውልቀህ ፍስሓን አለበስኸኝ፤ 12እንግዲህ ነፍሴ ታመስግንህ፤ ዝምም አትበል፤ እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤ ለዘላለም አመሰግንሃለሁ።ምዕራፎች
1
2
3
4
5
6
7
8
9
10
11
12
13
14
15
16
17
18
19
20
21
22
23
24
25
26
27
28
29
30
31
32
33
34
35
36
37
38
39
40
41
42
43
44
45
46
47
48
49
50
51
52
53
54
55
56
57
58
59
60
61
62
63
64
65
66
67
68
69
70
71
72
73
74
75
76
77
78
79
80
81
82
83
84
85
86
87
88
89
90
91
92
93
94
95
96
97
98
99
100
101
102
103
104
105
106
107
108
109
110
111
112
113
114
115
116
117
118
119
120
121
122
123
124
125
126
127
128
129
130
131
132
133
134
135
136
137
138
139
140
141
142
143
144
145
146
147
148
149
150