መዝሙር
ምዕራፎች 9
መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም
በክፉ ላይ ፍርድ
ለመዘምራን አለቃ፤ በሙትላቤን ቅኝት፤ የዳዊት መዝሙር
1 እግዚአብሔር ሆይ፤ በፍጹም ልቤ አመሰግንሃለሁ፤ስለ ድንቅ ሥራዎችህም ሁሉ እናገራለሁ። 2በአንተ ደስ ይለኛል፤ ሐሤትም አደርጋለሁ፤ልዑል ሆይ፤ ስምህን በመዝሙር እወድሳለሁ። 3ጠላቶቼ ወደ ኋላ በተመለሱ ጊዜ፣ተሰነካክለው ከፊትህ ይጠፋሉ፤ 4ፍርዴም ጒዳዬም በአንተ እጅ ናቸውና፤ቅን ፍርድ እየሰጠህ በዙፋንህ ላይ ተቀምጠሃል። 5ሕዝቦችን ገሠጽህ፤ ክፉዎችንም አጠፋህ፤ስማቸውንም እስከ ወዲያኛው ደመሰስህ። 6ጠላቶች ለዘላለም ጠፉ፤ከተሞቻቸውንም ገለባበጥሃቸው፤መታሰቢያቸውም ተደምስሶአል። 7 እግዚአብሔር ግን ለዘላለም በዙፋኑ ላይ ነው፤መንበሩንም ለፍርድ አጽንቶአል። 8ዓለምን በጽድቅ ይዳኛል፤ሕዝቦችንም በፍትሕ ይገዛል። 9 እግዚአብሔር ለተጨቈኑት ዐምባ ነው፤በመከራም ጊዜ መጠጊያ ይሆናቸዋል። 10ስምህን የሚያውቁ ይታመኑብሃል፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ የሚሹህን አትተዋቸውምና። 11በጽዮን ለሚኖር ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤ሥራውንም በሕዝቦች መካከል በግልጽ አውሩ፤ 12ደም ተበቃዩ ዐስቦአቸዋልና፤የጭቍኖችንም ጩኸት አልዘነጋም። 13 እግዚአብሔር ሆይ፤ ጠላቶቼ የሚያደርሱብኝን መከራ ተመልከት፤አይተህም ራራልኝ፤ ከሞት ደጅም አንሥተህ መልሰኝ፤ 14ይህን ስታደርግልኝ፣ በጽዮን ሴት ልጅ ደጅ፣ምስጋናህን ዐውጃለሁ፤በማዳንህም ሐሤት አደርጋለሁ። 15አሕዛብ በቈፈሩት ጒድጓድ ገቡ፤እግራቸውም ራሳቸው በስውር ባስቀመጡት ወጥመድ ተያዘ። 16 እግዚአብሔር በትክክለኛ ፍርዱ የታወቀ ነው፤ክፉዎችም በእጃቸው ሥራ ተጠመዱ። ሒጋዮን ሴላ 17ክፉዎች ተመልሰው ወደ ሲኦል ይወርዳሉ፤እግዚአብሔርን የሚዘነጉ ሕዝቦችም ሁሉ እንደዚሁ። 18ችግረኞች ግን መቼም ቢሆን አይረሱም፤የድኾችም ተስፋ ለዘላለም መና ሆኖ አይቀርም። 19 እግዚአብሔር ሆይ ተነሥ፤ ሰውም አያይል፤አሕዛብም በፊትህ ይፈረድባቸው። 20 እግዚአብሔር ሆይ፤ ድንጋጤ አምጣባቸው፤ሕዝቦች ሰው ከመሆን እንደማያልፉ ይወቁ። ሴላምዕራፎች
1
2
3
4
5
6
7
8
9
10
11
12
13
14
15
16
17
18
19
20
21
22
23
24
25
26
27
28
29
30
31
32
33
34
35
36
37
38
39
40
41
42
43
44
45
46
47
48
49
50
51
52
53
54
55
56
57
58
59
60
61
62
63
64
65
66
67
68
69
70
71
72
73
74
75
76
77
78
79
80
81
82
83
84
85
86
87
88
89
90
91
92
93
94
95
96
97
98
99
100
101
102
103
104
105
106
107
108
109
110
111
112
113
114
115
116
117
118
119
120
121
122
123
124
125
126
127
128
129
130
131
132
133
134
135
136
137
138
139
140
141
142
143
144
145
146
147
148
149
150