134 ትእዛዝህን መጠበቅ እንድችል፣ከሰዎች ጥቃት ታደገኝ።
135 በባሪያህ ላይ ፊትህን አብራ፤ሥርዐትህንም አስተምረኝ።
136 ሕግህ ባለመከበሩ፤እንባዬ እንደ ውሃ ይፈሳል።
137 እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ጻድቅ ነህ፤ፍርድህም ትክክል ነው።
138 ምስክርነትህን በጽድቅ አዘዝህ፤እጅግ አስተማማኝም ነው።
139 ጠላቶቼ ቃልህን ዘንግተዋልና፣ቅናት አሳረረኝ።
140 ቃልህ እጅግ የነጠረ ነው፤ባሪያህም ወደደው።