137 እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ጻድቅ ነህ፤ፍርድህም ትክክል ነው።
138 ምስክርነትህን በጽድቅ አዘዝህ፤እጅግ አስተማማኝም ነው።
139 ጠላቶቼ ቃልህን ዘንግተዋልና፣ቅናት አሳረረኝ።
140 ቃልህ እጅግ የነጠረ ነው፤ባሪያህም ወደደው።
141 እኔ ታናሽና የተናቅሁ ነኝ፤ነገር ግን መመሪያህን አልዘነጋሁም።
142 ጽድቅህ ዘላለማዊ ጽድቅ ነው፤ሕግህም እውነት ነው።
143 መከራና ሥቃይ ደርሶብኛል፤ነገር ግን ትእዛዝህ ደስታዬ ነው።