139 ጠላቶቼ ቃልህን ዘንግተዋልና፣ቅናት አሳረረኝ።
140 ቃልህ እጅግ የነጠረ ነው፤ባሪያህም ወደደው።
141 እኔ ታናሽና የተናቅሁ ነኝ፤ነገር ግን መመሪያህን አልዘነጋሁም።
142 ጽድቅህ ዘላለማዊ ጽድቅ ነው፤ሕግህም እውነት ነው።
143 መከራና ሥቃይ ደርሶብኛል፤ነገር ግን ትእዛዝህ ደስታዬ ነው።
144 ምስክርነትህ ለዘላለም የጽድቅ ምስክርነት ነው፤በሕይወት እኖር ዘንድ ማስተዋልን ስጠኝ።
145 እግዚአብሔር ሆይ፤ በፍጹም ልቤ እጮኻለሁና መልስልኝ፤ሥርዐትህንም እጠብቃለሁ።