149 እንደ ቸርነትህ መጠን ድምፄን ስማ፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ ሕግህ መልሰህ ሕያው አድርገኝ።
150 ደባ የሚያውጠነጥኑ ወደ እኔ ቀርበዋል፤ከሕግህ ግን የራቁ ናቸው።
151 እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ግን ቅርብ ነህ፤ትእዛዛትህም ሁሉ እውነት ናቸው።
152 ለዘላለም እንደ መሠረትሃቸው፣ከጥንት ምስክርነትህ ተረድቻለሁ።
153 ሕግህን አልረሳሁምና፣ ሥቃዬን ተመልከት፤ ታደገኝም።
154 ተሟገትልኝ፤ አድነኝም፤እንደ ቃልህም ሕያው አድርገኝ።
155 ሥርዐትህን ስለማይሹ፣ድነት ከክፉዎች የራቀ ነው።