5 ሥርዐትህን እጠብቅ ዘንድ፣ምነው መንገዴ ጽኑ በሆነልኝ ኖሮ!
6 ወደ ትእዛዛትህ ስመለከት፣በዚያን ጊዜ አላፍርም።
7 የጽድቅ ፍርድህን ስማር፣በቅን ልብ ምስጋና አቀርብልሃለሁ።
8 ሥርዐትህን እጠብቃለሁ፤ፈጽመህ አትተወኝ።
9 ጒልማሳ መንገዱን እንዴት ያነጻል?በቃልህ መሠረት በመኖር ነው።
10 በሙሉ ልቤ ፈለግሁህ፤ከትእዛዛትህ ፈቀቅ እንዳልል አድርገኝ።
11 አንተን እንዳልበድል፣ቃልህን በልቤ ሰወርሁ።