9 ዙሪያዬን የከበቡኝ ሰዎች ራስ፣የከንፈራቸው መዘዝ ይጠምጠምበት።
10 የእሳት ፍም በላያቸው ይውረድ፤ዳግመኛም እንዳይነሡ ወደ እሳት ይጣሉ፤ማጥ ወዳለበት ጒድጓድ ይውደቁ።
11 ምላሰኛ በምድሪቱ ጸንቶ አይኑር፤ዐመፀኛውን ሰው ክፋት አሳዶ ያጥፋው።
12 እግዚአብሔር ለድኻ ፍትሕን እንደሚያስከብር፣ለችግረኛውም ትክክለኛ ፍርድን እንደሚሰጥ ዐውቃለሁ።
13 ጻድቃን በእውነት ስምህን ያመሰግናሉ፤ቅኖችም በፊትህ ይኖራሉ።