7 በሂሶጵ እርጨኝ፤ እኔም እነጻለሁ፤እጠበኝ፤ ከበረዶም ይልቅ ነጭ እሆናለሁ።
8 ሐሤትንና ደስታን አሰማኝ፤ያደቀቅሃቸው ዐጥንቶቼም ደስ ይበላቸው።
9 ፊትህን ከኀጢአቴ መልስ፤በደሌንም ሁሉ ደምስስልኝ።
10 አምላኬ ሆይ፤ ንጹሕ ልብ ፍጠርልኝ፤ቀና የሆነውንም መንፈስ በውስጤ አድስ።
11 ከፊትህ አትጣለኝ፤ቅዱስ መንፈስህንም ከእኔ ላይ አትውሰድ።
12 የማዳንህን ደስታ መልስልኝ፤በእሽታ መንፈስም ደግፈህ ያዘኝ።
13 እኔም ለሕግ ተላላፊዎች መንገድህን አስተምራለሁ፤ኀጢአተኞችም ወደ አንተ ይመለሳሉ።