1 የሰራዊት አምላክ ሆይ፤ማደሪያህ ምንኛ የተወደደ ነው!
2 ነፍሴ የእግዚአብሔርን አደባባዮች ትናፍቃለች፤እጅግም ትጓጓለታለች፤ልቤና ሥጋዬም፣ለሕያው አምላክ እልል በሉ።
3 ንጉሤና አምላኬ የሰራዊት አምላክ ሆይ፤መሠዊያህ ባለበት ስፍራ፣ድንቢጥ እንኳ መኖሪያ ቤት፣ዋኖስም ጫጩቶቿን የምታኖርበት ጐጆ አገኘች።
4 በቤትህ የሚኖሩ የተባረኩ ናቸው፤እነርሱም ለዘላለም ያመሰግኑሃል። ሴላ
5 አንተን ብርታታቸው ያደረጉ፣በልባቸው የጽዮንን መንገድ የሚያስቡ ቡሩካን ናቸው።