152 ለዘላለም እንደ መሠረትሃቸው፣ከጥንት ምስክርነትህ ተረድቻለሁ።
153 ሕግህን አልረሳሁምና፣ ሥቃዬን ተመልከት፤ ታደገኝም።
154 ተሟገትልኝ፤ አድነኝም፤እንደ ቃልህም ሕያው አድርገኝ።
155 ሥርዐትህን ስለማይሹ፣ድነት ከክፉዎች የራቀ ነው።
156 እግዚአብሔር ሆይ፤ ርኅራኄህ ታላቅ ነው፤እንደ ሕግህ ሕያው አድርገኝ።
157 የሚያሳድዱኝ ጠላቶቼ ብዙዎች ናቸው፤እኔ ግን ከምስክርህ ዘወር አላልሁም።
158 ቃልህን አይጠብቁምና፣ከዳተኞችን አይቼ አርቃቸዋለሁ።