154 ተሟገትልኝ፤ አድነኝም፤እንደ ቃልህም ሕያው አድርገኝ።
155 ሥርዐትህን ስለማይሹ፣ድነት ከክፉዎች የራቀ ነው።
156 እግዚአብሔር ሆይ፤ ርኅራኄህ ታላቅ ነው፤እንደ ሕግህ ሕያው አድርገኝ።
157 የሚያሳድዱኝ ጠላቶቼ ብዙዎች ናቸው፤እኔ ግን ከምስክርህ ዘወር አላልሁም።
158 ቃልህን አይጠብቁምና፣ከዳተኞችን አይቼ አርቃቸዋለሁ።
159 መመሪያህን እንዴት እንደምወድ ተመልከት፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ ምሕረትህ ሕያው አድርገኝ።
160 ቃልህ በሙሉ እውነት ነው፤ጻድቅ የሆነው ሕግህም ዘላለማዊ ነው።