3 ዐመፅን አያደርጉም፤ነገር ግን በመንገዱ ይሄዳሉ።
4 ጠንቅቀን እንጠብቃት ዘንድ፣አንተ ሥርዐትን አዘሃል።
5 ሥርዐትህን እጠብቅ ዘንድ፣ምነው መንገዴ ጽኑ በሆነልኝ ኖሮ!
6 ወደ ትእዛዛትህ ስመለከት፣በዚያን ጊዜ አላፍርም።
7 የጽድቅ ፍርድህን ስማር፣በቅን ልብ ምስጋና አቀርብልሃለሁ።
8 ሥርዐትህን እጠብቃለሁ፤ፈጽመህ አትተወኝ።
9 ጒልማሳ መንገዱን እንዴት ያነጻል?በቃልህ መሠረት በመኖር ነው።