38 ትፈራ ዘንድ፣ለአገልጋይህ የገባኸውን ቃል ፈጽም።
39 የምፈራውን መዋረድ ከእኔ አርቅ፤ደንብህ መልካም ነውና።
40 እነሆ፤ ድንጋጌህን ናፈቅሁ፤በጽድቅህ ሕያው አድርገኝ።
41 እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህ ወደ እኔ ይምጣ፤ማዳንህም እንደ ቃልህ ይላክልኝ።
42 በቃልህ ታምኛለሁና፣ለሚሰድቡኝ መልስ እሰጣለሁ።
43 ሕግህን ተስፋ አድርጌአለሁና፣የእውነትን ቃል ከአፌ ፈጽመህ አታርቅ።
44 ከዘላለም እስከ ዘላለም፣ሕግህን ዘወትር እጠብቃለሁ።