56 ሥርዐትህን እከተላለሁ፤ይህችም ተግባሬ ሆነች።
57 እግዚአብሔር ዕድል ፈንታዬ ነው፤ቃልህን ለመታዘዝ ቈርጫለሁ።
58 በፍጹም ልቤ ፊትህን ፈለግሁ፤እንደ ቃልህ ቸርነትህን አሳየኝ።
59 መንገዴን ቃኘሁ፤አካሄዴንም ወደ ምስክርህ አቀናሁ።
60 ትእዛዝህን ለመጠበቅ፣ቸኰልሁ፤ አልዘገየሁምም።
61 የክፉዎች ገመድ ተተበተበብኝ፤ እኔ ግን ሕግህን አልረሳሁም።
62 ስለ ጻድቅ ሥርዐትህ፣በእኩለ ሌሊት ላመሰግንህ እነሣለሁ።