21 እግዚአብሔር ሆይ፤ የሚጠሉህን አልጠላምን?በአንተ ላይ የሚነሡትንስ አልጸየፍምን?
22 በፍጹም ጥላቻ ጠልቻቸዋለሁ፤ባላጋራዎቼም ሆነዋል።
23 እግዚአብሔር ሆይ፤ መርምረኝ፤ ልቤንም ዕወቅ፤ፈትነኝ፤ ሐሳቤንም ዕወቅ፤
24 የክፋት መንገድ በውስጤ ቢኖር እይ፤በዘላለምም መንገድ ምራኝ።