1 እግዚአብሔር ሆይ፤ ከክፉ ሰዎች አድነኝ፤ከዐመፀኞችም ሰዎች ጠብቀኝ፤
2 እነርሱ በልባቸው ክፉ ነገር ያውጠነጥናሉ፤በየዕለቱም ጦርነት ይጭራሉ።
3 ምላሳቸውን እንደ እባብ ያሾላሉ፤ከከንፈራቸውም በታች የእፉኝት መርዝ አለ። ሴላ
4 እግዚአብሔር ሆይ፤ ከክፉዎች እጅ ጠብቀኝ፤እግሮቼንም ለመጥለፍ ከሚያደቡ ዐመፀኞች ሰውረኝ።
5 ትዕቢተኞች ወጥመድ በስውር አስቀመጡብኝ፤የመረባቸውን ገመድ ዘረጉብኝ፤በመንገዴም ላይ አሽክላ አኖሩ። ሴላ
6 እግዚአብሔር ሆይ፤ “አንተ አምላኬ ነህ” እልሃለሁ፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ የልመና ጩኸቴን ስማ።