4 እንደ ሥራቸው፣እንደ ክፉ ተግባራቸው ክፈላቸው፤እንደ እጃቸው ሥራ ስጣቸው፤አጸፋውን መልስላቸው።
5 ለእግዚአብሔር ሥራ ግድ ስለሌላቸው፣ለእጆቹም ተግባራት ስፍራ ስላልሰጡ፣እርሱ ያፈርሳቸዋል፤መልሶም አይገነባቸውም።
6 የልመናዬን ቃል ሰምቶአልና፣ እግዚአብሔር የተባረከ ይሁን።
7 እግዚአብሔር ብርታቴና ጋሻዬ ነው፤ልቤ በእርሱ ይታመናል፤ እርሱም ዐግዞኛል፤ልቤ ሐሤት አደረገ፤በዝማሬም አመሰግነዋለሁ።
8 እግዚአብሔር ለሕዝቡ ብርታታቸው ነው፤ለቀባውም የመዳን ዐምባ ነው።
9 ሕዝብህን አድን፤ ርስትህንም ባርክ፤እረኛ ሁናቸው፤ ለዘላለሙም ዐቅፈህ ያዛቸው።