6 ግፍን ያውጠነጥናሉ፤ደግሞም፣ “የረቀቀች ሤራ አዘጋጅተናል” ይላሉ፤አቤት! ልቡ፣ አእምሮውም እንዴት ጥልቅ ነው!
7 እግዚአብሔር ግን በፍላጻው ይነድፋቸዋል፤እነርሱም ድንገት ይቈስላሉ።
8 በገዛ ምላሳቸው ያሰናክላቸዋል፤ጥፋትንም ያመጣባቸዋል፤የሚያዩአቸውም ሁሉ በትዝብት ራሳቸውን ይነቀንቃሉ።
9 የሰው ልጆች ሁሉ ይፈራሉ፤የእግዚአብሔርን ሥራ በይፋ ያወራሉ፤ያደረገውንም በጥሞና ያሰላስላሉ።
10 ጻድቅ በእግዚአብሔር ደስ ይበለው፤እርሱንም መጠጊያ ያድርገው፤ልበ ቅኖችም ሁሉ ደስ ይበላቸው።